Tuesday, December 22, 2015

የአገር ፍቅር ፋና፤

እኔ የዘጠና ሁለት ዓመት አዛዉንት ነኝ፤ ከሃገሬ ከኢትዮጵያና ከህዝቧ ደህንነትና እድገት፤ ሰላምና ነጻነት፤ ድሮም ዛሬም
የመፈልገው ነገር የሌም። ህይዎቴን በሙሉ ያሳለፍኩት እክሌ ከእከሌ ሳልለይ አገሬን ህዝቤን በማገልገል ነው። ከልዩ ልዩ የኢትዮጵያ ጎሳዎች የተዋለድኩ የተዛመድኩ ”ተዋህዶ ክርስትያን አማራ” ኢትዮጵያዊ ነኝ።

ከቅርብ ጊዜ ጀምሮ አማራዉን ለማጥፋት፤ ከኢትዮጵያ ለማቃቃርና ለመለያየት የተጀመረው ዘመቻ አሁንም እየቀጠለ
ነው፤ አገር ዉስጥ ቦታ የላችሁም ተከለሉ እንባላለን፤ ሴቶቻችን ኢየተፈነገሉ በችጋር ግፊት ለባርነትና ለዝሙት ለአረብ አገር እየተሸጡ ነው፤ ወንዱም ሴቱም ኢየተባረረ ስደትኛ ወይም የርካሽ ጉልበት ምንጭ ሆኗል፤ ያልተከሰስነው
ያልተወንጄልነው ሃጥያት የለም፤ ጡት ቆራጭ ሰላቢ ተብለናል፤ በሽታ የሚከላከልክትባት ኢየተባለ በአማራው አገር ላሉ
ኢህቶቻችን የምያመክን መድሃኒት ክትባት እየተሰጠ የአማራው ህዝብ ቁጥር በሚልዮን እንዲቀነስ ተደርጓል፤ በየአይነቱ

 ግፍ ሲደርግብን በጊዜ ያልፋል ብለን ታግሰን ነበር፤ አሁን ግን በቃ ብለናል።

በምንም መንገድ ስልጣን የሚፈልጉ ፖሊካኞች አብረን ዎያኔን እንዉጋ ይሉናል፤ ነገር ግን እኛ የምናውቀው አንድነት በሃቅና በእኩልነት ሲመሰረት ነው፤ ኢኛ የምንመኛት የምንሞትላት ኢትዮጵያ ሁሉም ዜጋ በነጻንት መብቱ በህግ
ተጠብቆ፤ በኢትዮጵያ ጠረፍ ዉስጥ የትም ሂዶ፣ የትም ዉሎ፤ የትም ሰርቶ፤ የትም አፍርቶ፤ የሚኖርባት አገር ስትሆን
ንው። ብርሃብ በበሽታ በችጋር በደሀየ በተራበ ህዝብ ላይ የፖሊቲካ ገበያተኞችና የውጭ ግርፍ ወረበሎች የሚሻሻጡባት የገበያ ሸቀጥ ስትሆን አይደለም። ሲለዚህ እኝ አማሮች ለሃገራችን ያለንን ግዴታ ለመፈጸም ከሁሉ አስቀድሞ ራሳችንን
በህብረት በማደራጀትና በማጠናቀር፤ ብርቱ ሃይል ምቋቋም አለብን፤ በደካማነት እኳን አገርን ራሳችንንም ከጥፋት

ለማዳን እንደማንችል ግልጽ ነው።

እንዲሁ የተከበራችሁ እናቶች እህቶች ሴት ውጣቶች ኢትዮጵያ እኮ አንቺ የምትባለው በናንተ ጾታ ነው፤ ምጣችሁ
ተሰቃይተችሁ ወልዳችሁ፤ ቤተሰቡን አቅፋችሁ ጠብቃችሁ የምታኖሩ እናንተ ናችሁ፤ በኢትዮጵያ ታሪክ ያላችሁ ከፍተኛ ሚናና ትግባር የነጻነትዋ መሰረት ነው፤ በታሪክ እንደሚባለው “ ርሳ አሊ ለአማቻቸው ለተዎድሮስ ለፋሲካ አንድ ወርች ልከውላቸው ተቀይመዉ ለሚስታቸው ለምንትዋብ ‘አይሽ አባትሽ የሚያደርጉኝን’ ብለው በቢስጭት ቢነግሯቸው
ምንትዋብ ‘ታድያ ተነሳ ምን ተጠብቃለህ ‘ ቢሏቸው ነው የሸፈቱት ተበሎ ይነገራል። የኢትዮጵያን ሴቶች ጉብዝናና ብልትሙና መዘረዘር አያሻም የታወቀ ነው፡ በዛሬ ወቅት ደግሞ በብዙ ዓይነት ገጽ የተማሩ የላቁ የተሰማሩ ባለሞያዎች ናቸው፤ የአገር አናቶች ናችሁ ተንሱ አስነሱ እያልኩ እማለዳለሁ።

ኢድል በማጣት እንጂ ሰው ደሃ ሁኖ አይፈጠርም፤ የኢትዮጵያ ህዝብ መንፈሳዊና ባህላዊ ኢሰቶች ከማንም ብሔረሰብ
አያንሱም፤ ህዝባችን ብሩህ ተታሪ ትጉ ባለሞያ ነው፤ የሁለት ታላላቅ ሃይማኖቶች ባለአደራ ሁኖ በማንም ሳይገዛ ብዙ ሺ ዘመናት ነጻነቱን ጠብቆ ኖርዋል፤ ለዚህ ራዥም የነጻነት ትግል ብዙ ምስዋእት አድርጓል፤ አጉል እድል እየደረሰበት
እድገቱንም አዘግይቷል፡ አሁን ደግም በከተምንበት በኖርንበት አገር የፈረንጅ ግርፊት ወሮበሎች ተነስተው ባእድ ናችሁ
ቦታም የላችሁ ይሉናል፡ ዛሬ ደሞ ዙረው ኢንደምያርዱን እያወቅን አብረን ኢንዝመት ይሉናል።

 ዝምታችን ትግስታችን ሞኝነት መስሏቸዋል።

አዎን ለሕዝባችንና ለሃገራችን ነጻነትና ህልዉና እንታገላለን እንሞታለን፤ እርስ በራሳችን ሊለያዩንና ሊያቃቃሩን
የሚፈልጉትን መንጋዎች አንቃወማለን፤ በምሳሌ የአማአራና የኦሮሞ ጎሳዎች ከአምስት መቶ ዓመት (፭መቶ) ይበልጥ
አብረው ኖረዋል ተጋብተዋል ተዛምደዋል፤ ኢንዲሁም ከሌሎቹ የኢትዮጵያ ጎሳዎች ተዛምደዉና ተባብረው አገራⶨዉን ኢትዮጵያን በነጻነት አስከብረው ቆይተዋል፤ ይሄም ታሪክ የሚመሰክረው ሃቅ ነው፤ እንደዚሁ የትግራይ ሕዝብ ስጋችን ወንድማችን ነው፤ የወያኔን ወመኔዎች የምናቃወመው ስልጣን የዘው ሃገራⶭንንና አንድነታችንን በማፍረስ፤ ሃብትዋን
በመዝረፍና በማራከስ፤ ሰፊዉን ህብረሰቡ በማቆርቆዝና በሃይል መጨኮንና በግፍ ህገ ቢስ በሙስና የተለወሰ አስተዳድር
በማድረጋቸው፤ ለዉጭ ሃይሎችና ነጋዴውች አግሪትዋን በመሸጥቸው ነው። አሁን ይህ የግፍና የዉንብድና አገዛዝ በቃው ብለናል። የዎሬ ዘመን አልፏል ይትግባር ጊዜ ነው።

አማራ ተነስ መብትህን ጠብቅ፤ የአትዮጵያ ሕዝብ ተነስ አለኝታህንና ነጻነትህን አስከብር ኢላለሁ።
እ፤ዘ፤ ትሕሳስ ፪ሺ፰
///////////// ************ //////////// ************ ////////////

No comments:

Post a Comment